2013 ሜይ 2, ሐሙስ

የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ወግ - ከበውቀቱ ስዩም

ማለዳ መነሣት አልወድም፡፡ዛሬ ግን አቡነ ጴጥሮስ ከመታሰቢያቸው ዙፋን ሲወርዱ ለመታዘብ በማለዳው ካልጋየ ጨክኘ ወረድሁ፡፡ለአቡነ ጴጥሮስ ፍቅር ስል የማለዳ እንቅልፌን ብሰዋ አይቆጨኝም፡፡በቅርቡ በሚከፈተው ጦማሬ ላይ ስለ ጀግናው ጴጥሮስ በሰፊው የመጻፍ ሐሳብ አለኝ፡፡ በቦታው ስደርስ፣የጴጥሮስ ሀውልት በጣውላ ተገንዞ ቆሟል፡፡ድብርት ተጫጫነኝ፡፡ምናልባት አያቶቼ አቡኑ ሲረሸኑ በተመለከቱበት ሰአት የተሰማቸው ስሜት እንዲህ ሳይሆን አይቀርም፡፡ የራስ ቁር የደፉ የቀን ሠራተኞች በአቡኑ ትክሻ ላይ እንደ ወፍ ሰፍረዋል፡፡ ወደ መርካቶ በሚሄዱ ተሳፋሪዎች የተሞሉ ሚኒባሶች አደባባዩን ታክከው ሽው ይላሉ፡፡ ተሳፋሪዎቹ፣ በመስታውት አሻ...ግረው የሚመለከቱት ትእይንት ብዙ የመሰጣቸው አይመሰልም፡፡በፋሲካ አስፈሪ የዶሮ ዋጋ ለተጠመደ አእምሮ ታሪክ ምኑ ነው?? ከተመልካቹ በላይ የፖሊሱ ቁጥር የሚበልጥ መሰለኝ፡፡አንድ ፒካፕ መኪና ስትበር መጣችና ቁና ሙሉ ፌደራል ፖሊስ አራገፈች፡፡ሰብሰብ ብለን በቆምንበት አንዱ ፖሊስ ጠጋ አለና‹‹ እናንተን አይመለከታችሁም ከዚህ ሂዱ›› አለ፡፡ካጠገቤ የቆመ ጎበዝ ‹‹ማየት መብታችን ነው›› ብሎ መልሶ ጮከበት፡፡አሀ! የጴጥሮስ መንፈስ አልከሰመም ማለት ነው፡፡ፖሊሱ ምንም ሳይመልስ ከሬድዮ መገናኛው ጋር እየተመካከረ ካካባቢው ራቀ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ጋዜጠኛ ጓደኞቼ ካሜራቸውን ታጥቀው ደረሱና ተቀላቀሉኝ፡፡ ሀውልቱን ማስቀረት ስላልቻሉ ምስሉን ቀርጸው ለማስቀረት ተሯሯጡ፡፡ ድንገት ቀና ብየ ሳይ ከሀውልቱ ፊትለፊት ጅማ በር የሚባል ፣ጣልያን የሠራው አሮጌ ሕንጻ ይታየኛል፡፡ባቡሩ የአቡነ ጴጥሮስን መታሰቢያ ደቅድቆ ሲያልፍ፣ጣልያን ሠራሹን ግንብ ንክች አያደርገውም፡፡ጉደኛ ባቡር!!! በጣውላ የተገነዘውን የአቡኑን ሀውልት ለመሸከም አንድ አዳፋ ረጅም ተጎታች መኪና ብቅ አለ፡፡ዳይኖሰር የመሰለ ክሬን ሀውልቱን ነቅሎ ሲያንጠለጥለው፣ሀውልቱ የነበረበት ቦታ ጥርስ የወለቀበት አፍ መሠለ፡፡ቀሪውን የማየት ፍላጎት ስላልነበረኝ ከጓደኛየ ጋር ወደ ፒያሳ አቀናሁ፡፡ብዙ ነገር እዬተለወጠ መሆኑን አየሁ፡፡የጥንቱ መሀሙድ መዚቃ ቤት ወደ ቡቲክ መቀየሩን አስተዋልሁ፡፡የጥንቱ አያሌው ሙዚቃ ቤት ፍራፍሬ መሸጫ ሱቅ ሆኗል፡፡ከጥቂት ወራት በፊት ብርቱካኔ የሚለው ሙዚቃ ይንቆረቆርበት የነበረው ቦታ ፣አሁን ብርቱካን በኪሎ ይሸጥበታል፡፡ አዲስአበባ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ያለጥርጥር፣ባቡር ይኖራታል፡፡ቀለበት መንገዶች ይኖሯታል፡፡አሪፍ ህንጻዎች ይኖሯታል፡፡ነገር ግን፣ ትናንት የሚባለው ነገር አይኖራትም፡፡ A city without past ላዲስ አበባ የተገባ ቅጽል ነው፡፡ ወደ ሰፈሬ የሚሄድ ታክሲ ስፈናጠጥ፣ የሚከተሉት የጸጋየ ገብረመድህን ግጥሞች ሽው አሉብኝ፡፡ ….መጭው ደመና ጥቁረቱ፣ ጮቁ ፣ማጡ፣የክረምቱ፣አቤት ዝቅጠቱ ማስፈራቱ የኛስ ትውልድ አከተመ፣አገራችንን አምክነን የነገስ ዘር ምን ይበለን፣ስንተወው ሲኦል አውርሰን

How can Ethiopia and Africa move away from aid dependence? BBC

By Alexis Akwagyiram, BBC News
Ethiopia, with its high growth rates, has an ambitious development plan
Much of Africa relies on foreign aid, despite economic growth in parts of the continent significantly outpacing the global average.
So, how is the money spent and how can countries move away from aid dependence?
Ethiopia has a split personality.
At first glance it seems to be on an unbroken upward trajectory.
Like a number of African countries, it has one of the fastest-growing economies in the world - expanding by about 10% a year since 2004.
And, in recent years, the country has attracted the attention of foreign investors.
Ethiopia has come a long way since images of drought and famine broadcast around the world prompted the Live Aid fundraising concerts of 1985.
But the country's growth does not tell the whole story.
Ethiopia remains one of the poorest countries on the planet.
About a third of the population earn less than $1 (63p) a day and it received $504m (£324m) from the UK government in 2011/12, making it the biggest recipient of bilateral aid from the country that year.
Ethiopia's ambassador to the UK, Berhanu Kebede, said aid - primarily from the UK, the European Union and African Development Bank - was used for healthcare, primary school education and the provision of clean drinking water.
It funds the training of more than 30,000 workers to provide grassroots health care - often in hard to reach rural areas. It also helps to pay the wages of primary school teachers.

African growth strategies

  • Under its Vision 2030 programme, Kenya plans to develop its technology hub - popularly referred to as Konza City - and its rail infrastructure
  • Uganda wants 80% of its population to have access to electricity and safe water within 30 years
  • Nigeria aims to be among the 20 most-developed economies in the world by 2020
  • Ethiopia is building a network of dams and wind turbines to generate electricity that it hopes will reach 70% of the country by 2016
Mr Kebede said his country was "embarking on a huge development programme" in a bid to reduce its reliance on aid.
"Aid plays a significant role but, generally, it's a declining trend," he said.
"I'm not trying to undermine the role of aid, but our main aim is to move from aid to trade and investment.
"Our target is to become a middle income country by 2020 and, by 2030, to be classed as developed."
Ethiopia hopes to meet its targets by investing in higher education, agriculture and its manufacturing sector.
The ambassador said the majority of its development plans were being funded from the government's own budget, rather than aid.
Thirty universities have been built since 1994 and four years ago the government introduced a target for 70% of students to study science, technology or engineering.
"Science and technology is the basis for the transformation of the country. We have to build expertise in these areas for the economy to take off."
He also said there were plans to use technology to improve productivity in agriculture, since most Ethiopians live in rural areas.
How long-term aid is helping Ethiopia's coffee farmers
"These are strategies that are geared towards tackling poverty by getting people into work and helping them to feed themselves. Development is going very well. We need to work hard to sustain this," said Mr Kebede.
In all, nearly half - 45% - of the UK's bilateral aid programme in 2011/12 was spent in Africa.
With many Western donors re-examining their foreign aid commitments as a result of economic downturns at home, changes are afoot and new alliances are being forged.
China is increasingly exerting its influence across Africa.
The Washington-based Center for Global Development and Aid Data has revealed research findings that suggest China is financing 1,673 development projects worth $75bn (£48bn) i...
Political decisions
Meanwhile, the UK has announced that it will stop giving direct aid to South Africa in 2015, arguing that the progress made since the end of apartheid means it no longer needs aid currently worth £19m a year.
While the decision to stop helping Africa's biggest economy seems relatively straightforward, decisions to allocate or halt aid can sometimes be politically charged.
Last year, a number of Western governments suspended aid to Rwanda after UN experts expressed concerns about its alleged support for the M23 militia in neighbouring Democratic Republic of Congo - something the country has long denied.
But Ethiopia, which has been accused of forcing tens of thousands of people off their land so it can be leased to foreign investors, still receives assistance. Like Rwanda, it has denied the claims.
Ethiopia has also become embroiled in the affairs of a neighbouring country - Somalia. However, its involvement - sending troops into Somalia to fight al-Shabab Islamist militants in 2011 - had the backing of the US.
The potential that can be found in the African diaspora is huge”
Ben Oguntala
John Rwangombwa from the Central Bank of Rwanda: "This is a vote of confidence in the Rwandan economy"
David Mepham, of Human Rights Watch, said the policies adopted by the UK's Department for International Development (DfID) towards Ethiopia and Rwanda appeared to be "inconsistent".
"DfID decided to withdraw all general budget support because of Rwandan support for the M23 in eastern Congo. Very serious rights abuses by the Ethiopian government have not triggered a comparable reassessment of DfID's strategy," he said.
"DfID and other donors remain unwilling to properly investigate serious rights abuses associated with the Ethiopian government's resettlement programme."
The withdrawal of aid can play a role in determining economic strategies.
Rwanda recently turned to the international financial markets to raise funds.
Last week it launched a $400m (£260m) 10-year bond sale which was heavily oversubscribed, attracting investor offers of more than $3bn (£1.9bn).
In doing so, it followed in the footsteps of several African countries - such as Ghana and Zambia - that have turned to the bond markets to raise capital.
The governor of the Central Bank of Rwanda, John Rwangombwa, told the BBC the move was part of its long-term development strategy.
'Unprecedented opportunity'
"We appreciate the support we get from our partners in terms of aid, but we think it's not sustainable as a long term development plan.
"That's why we have this ambitious development plan - to expedite our growth, expedite the size of our economy and be able to raise domestic resources to advance our development plan.
"We've had our taxes growing at a rate of 20% per year and we're sure that in the next five years we should be able to be considered as not aid dependant."
But the secret to building lasting economic development may lie somewhere else - beyond Western donors, China or even African countries themselves.
Research suggests Africans living outside the continent send more money home to their families than is sent by traditional ...
Ben Oguntala, a 39-year-old Londoner of Nigerian origin, wants to build on that flow of money entering the continent.
The trainee barrister is the driving force behind Developed Africa, a website which provides a platform through which people from Africa's diaspora can be matched with African government agencies and non-governmental organisations to invest in business opportunities across the continent.
"The potential that can be found in the African diaspora is huge. People in the diaspora have a sense of empathy and want to invest back home.
"If you take the power of remittance and apply it to investment, the diaspora could be a force to be reckoned with.
"The internet has presented us with an unprecedented opportunity to reach out to the continent."
Mr Oguntala argues that diaspora investors could contribute to the construction of buildings and roads across Africa.
He said his fledgling website has already received particular interest from expatriate Nigerians, Ghanaians, Kenyans and Zambians based in the UK and US.
"We have the capabilities, intelligence and the competence as well as the desire to achieve change in Africa."

2013 ኤፕሪል 24, ረቡዕ

US-BACKED EGYPT MILITARY “TO CONTROL NILE” | ISRAELI MEDIA

Egypt’s military, financed by the United States, has been preparing for what could be a war for control of the Nile.
Western intelligence sources said the military command has urged President Mohammed Morsi for a buildup meant to block any attempt to divert the Nile. They said the military envisioned a crisis with Ethiopia that could threaten water supplies to Egypt and Sudan.Ethiopia Egypt Nile river map
“For the Egyptian military and government, this is perhaps the most burning security issue today,” a source said.
The sources said Morsi has sought to form a military alliance with Sudan to prevent Ethiopia from constructing a dam along the Nile. The Renaissance Dam was meant to draw 84 billion cubic meters of water from the Nile, sufficient for hydroelectric power.
“The military has been preparing for the prospect that air strikes would be ordered to stop construction or simply destroy the Ethiopian dam,” the source said.
Egypt, which receives 60 percent of the river’s water, has insisted on preferential rights to the Nile. The sources said the Morsi regime was expected to issue a stark warning to Addis Ababa during its next session of the Egyptian-Sudanese-Ethiopian technical committee in late May 2013. The Nile is shared by 10 countries.
“Certain measures have to be followed to make sure that Ethiopia gets the water necessary for storage in the dam in line with Egypt’s consent and needs,” an Egyptian official told the state-owned Al Ahram daily on April 18.
The sources said Egyptian military planning was based on the delivery of the new F-16 Block 52 multi-role fighter from the United States. They said the Egyptian Air Force, expected to receive 20 such aircraft in 2013, has determined that the latest F-16 variant, which included extended fuel tanks, would enable an attack on the Ethiopian dam.
Egypt has determined that the Renaissance Dam would comprise a loss of between eight and 18 million cubic meters per year. The sources said Cairo has repeatedly warned the United States of the danger of the Ethiopian project.
“The U.S. input here is crucial, because its aircraft would be used for any military operation against Ethiopia,” the source said.
***********
Acknowledgements to AmharicTube.com who bought the news from MiddlesEast Newsline for $8 USD. Originally titled “Egypt Military Gears For Water War“.

2013 ኤፕሪል 6, ቅዳሜ

100 People Who Changed the World

This is a list of 100 people who have changed the world.

People Who Changed the World

# 95 Emperor H/selasse  but Ethiopia doesn't respect this leader

To check follow;   http://www.biographyonline.net/people/people-who-changed-world.html

christ 1. Jesus Christ (c.5BC - 30AD) Spiritual Teacher, central figure of Christianity.
christ 2. Thomas Jefferson (1743- 1826) 3rd President of US. Principle author of Declaration of Independence
christ 3. Mikhail Gorbachev (1931 - ) Leader of Soviet Union. Oversaw transition from Communism in Eastern Europe.
christ 4. Martin Luther King (1929 - 1968) Non-violent civil rights leader
christ 5. Nelson Mandela (1918 - ) Anti-apartheid leader. First President of democratic South Africa in 1994.
christ 6. Lord Buddha (c 563 - 483BC) Spiritual Teacher and founder of Buddhism.
christ 7. Winston Churchill (1874 - 1965) Prime Minister of Great Britain during Second World War.
christ 8. William Shakespeare (1564- 1616) English poet and playwright.
christ 9. Adolf Hitler (1889 - 1945) Dictator of Nazi Germany.
christ 10. Abraham Lincoln (1809 – 1865) President of US during civil war, helped end slavery.

የቀበጡ እለት ሞት አይገኝም ከቴዲ አፍሮ ወደ ቅዱስ ገብሬል (መልካምሰው አባተ)

ከአመታት በፊት አንድ ቀን በጣም አንቀለቀለኝ፡፡ ጠገብኩ፡፡ ድምፃዊ ቴዲ አፍሮን በመተቼት ጋዜጣ ላይ ፃፍኩ፡፡
ከአድናቂ ጋር የሚያጣላ ነገር እንዳልጻፈ ሰው በነጻነት በሰፈሬ እዞር ነበር፡፡ ደፋር እኮ ነኝ፡፡ ቴዲ አፍሮን
የሚያክል ‘ጣኦት’ ተችቶ በነፃነት መዞር? የእንጦጦን ነፋስ ለመቀበል ከአዲሱ ገበያ ተነስቼ ወደ ላይ
እንጎራደዳለሁ፤ በኩራት፡፡ የቴዲ አፍሮን ምስል የለበሱ አምስት ወጠምሻ ወጣቶች ተጠጉኝ፡፡ መጀመሪያ አልፈራሁም፡፡
ዙሪያዬን በአምስት ጎረምሳ ስታጠር ግን ተንቦቀቦኩ፡፡ አንገቴ ስር ጫማ ጥፊ ገብቶልኝ ከመውደቄ በፊት አንድ ዙር
አማተርኩ፡፡ ዙሪያዬን ከበውኛል፡፡ አጠር ቀጠን ያለውን አድናቂ ገፍትሬው ወደ ሰሜን ሸመጠጥኩ፡፡ ተከተሉኝ፡፡
ስንሮጥ እንጦጦ ደረስን፡፡ የጎጃምን መስመር ይዤ እፈተለክ ቀጠልኩ፡፡ እንዲህ እንደምሮጥ አላውቅም ነበር፡፡ ‹‹ሩጫ
ለነ ቀነኒሳ ብቻ የተሰጠ ፀጋ ይመስለኝ ነበር፡፡›› ስል እያሰብኩ እሮጣለሁ፡፡ አባራሪዎቼም ይከተሉኛል፡፡ የዋዛ
አድናቂዎች አልነበሩም፡፡
‹‹ምን ያህል ቢያደንቁት ነው? ወይኔ ሰውዬው! ትምህርት ትቼ ብዘፍን ኖሮ ልቡ እስክትፈርጥ ድረስ የሚሮጥልኝ
አድናቂ ይኖረኝ ነበር፡፡ አባቴ ግን ሸወደኝ፡፡ ተማር ተማር እያለ የብርም የአድናቂም ድሃ አደረገኝ፡፡ ወደትምህርት
ቤት ሂድ ከሚለኝ እንደ አቶ አፍሮ ወደ አገር ቤት እያልክ ዝፈን ቢለኝ ምን ነበረበት?›› ስል እየተቆጨኹ
እሮጣለሁ፡፡ ሩጫ ከቁጭት ጋር አይሄድም፤ ያደክማል፡፡  ….ብቻ እንደ ቀነኒሳ ኋላዬን ገልመጥ እያልኩ እያየሁ እሮጣለሁ፡፡
ሱሉልታን አለፍኩ፡፡ አቤት ዳገቱ፡፡ ሮጥኩ፡፡ ሮጥኩ፡፡ ሮጥኩ፡፡ ሰላሌ ሜዳ ላይ ስደርስ ሩጫዬን ጨረስኩ፡፡ ሰው
እንዴት ዳገቱን አልፎ ሜዳው ላይ ሲደርስ ሩጫውን ይገታል? ተስፋ ቆረጥኩ፡፡ ተስፋ በቆረጠ ሁናቴ ወደ ኋላ ዞር ብዬ
ሳማትር አባራሪዎቼም ሩጫቸውን ጨርሰው ኖሯል፡፡ ተመስጌን አልኩ፡፡ አንደኛው ብቻ ተስፋ በመቁረጥና ተስፋ በማድረግ
መካከል ሆኖ ልሩጥ ልተወው እያለ በጥቂት ሜትሮች ከእኔ ኋላ ቆሟል፡፡ ትንሽ ቢሮጥ እኔ ነዳጅ ስላልነበረኝ ሊይዘኝ
ይችል ነበር፡፡ እግዚሃር ይስጠው መሮጡን ትቶ መሳደብ ጀመረ፡፡ ‹‹ቆይ ጠብቅ አንተ ውሻ! አንተ ነህ ቴዲዬን
የምትሳደበው? ሽንታም! ፈሳም! በቀቀን!…..፡፡ ስማ ደግሞ በዛው ንካው ወዳገርህ ወደ በጌ ምድር፡፡ በግ የበግ
ልጅ እንዲሁም የፍየል፡፡ ገበሬ ነህና ወደ ግብርና ትመለሳለህ እንጅ አዲሳባን ዳግም አትረግጣትም፡፡……›› አለና
ግራ ኋላ ዞሮ ተመለሰ፡፡ እኔም መንገድ ዳር ቆሜ ከበጌ ምድር አቅጣጫ የሚመጣ መኪና እጠብቅ ጀመር፡፡ አንድ እንጨት
የጫነ አይሱዙ ከጎጃም ሲመጣ አየሁ፡፡ ሲደርስ እጄን አውለበለብኩለት፡፡ ሾፌሩ አቆመልኝ፡፡ ‹‹ጋቢና ሙሉ ስለሆነ
ከላይ ውጣ!› አለኝ ሾፌር፡፡ ወጣሁ፡፡ አይሱዚው ትንሽ እንደሮጠ አሯሩጠውኝ ከተመለሱት አድናቂዎች ጋር ደረሰ፡፡
አባራሪዎቼ የመንገድ ዳር ይዘው ወዳገራቸው ወክ ያደርጋሉ፡፡ አይሱዚው እና እኔ አጠገባቸው ስንደርስ እጄን
አውለበለብኩላቸው፡፡ ባለማመን እና በንዴት ፊታቸው ጉበት ሲመስል ታዬኝ፡፡ ወደ አዲሳባ ቀድሜያቸው ስመለስ እኔን
የተሰማኝ ሃሴት እነሱን የተሰማቸው ንዴት ቢጋጭ 6 ሺ ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኤነርጂ ይፈጥር ነበር፡፡ አጋነንኩ
እንዴ? እሺ 60 ሺ ይሁን፡፡
አንደኛው አድናቂ አይሱዚው ላይ መሆኔንም እያዬ በሩጫም ሊከተለኝ አማረው፡፡ ሮጠ፡፡ ቆይቶ ሲያስበው መኪና ላይ ነው
ያለሁት፡፡ ሩጫውን አቆመ፡፡ ቢሮጥ ፈልጌ ነበር፡፡ ምናልባትም ፈጣን ሯጭ ሆኖ አይሱዚውን ሊደርስበት ይችል ይሆን
ነበር፡፡ ይህም ማለት አገሬ የ800 ሜትር ሯጭ አገኘች ማለት ይሆን ነበር፡፡ ከአድናቂነት ወደ ተደናቂነትም
ይሸጋገር ነበር፡፡ ለጀግና በመዝፈን ጀግንነቱን ያስመሰከረው እና አጥር ያልተበጀለት የዝና ኢምፓዬር የመሰረተው ቴዲ
አፍሮም ይዘፍንለት ነበር፡፡
*
*****                           *
በሌላ አንድ ቀን ማለትም በቀደም አራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ቁጭ ብዬ ሻይ እየጠጣሁ የቀጠረኝን ጓደኛዬን
እጠብቃለሁ፡፡ አንድ የራሱን ምስል በቲሸርት አሳትሞ የለበሰ ወጣት ወደ እኔ መጣ፡፡ ሰላም አለኝ፡፡ ሰላም
አልሁት፡፡ ተሰላለምን፡፡
‹‹አስታወስከኝ?›› አለ፡፡
‹‹ãረ በፍፁም!››
‹‹አንዴ ቴዲ አፍሮን በጋዜጣ ተችተኸው ከጓደኞቼ ጋር ልንደበድብህ ስናባርርህ ነበር፡፡ ትዝ አለህ?››
‹‹አሃ፤ ትዝ አለኝ፡፡ እና አሁንም እንሯሯጥ እያልከኝ ነው?›› አልኩት፡፡
ሳቀ፡፡
‹‹ቁጭ በል፤ ቁጭ ብለህ አውራኝ!››
ተቀመጠ፡፡
‹‹በውነቱ ያኔ ተሳስተናል፡፡ በእኔና በጓደኞቼ ስም ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ መለስ ዜናዊ የሰጠህን የመፃፍ መብት እኛ
ልንነጥቅህ መነሳታችን መለስን ቅዱስ እኛን እርኩስ ያደርጋል፡፡ ኦባማ እንዳለው የመፃፍ መብትን በመንፈግ ከመለስ
ዜናዊ አንሶ መገኘት ማለት ደግሞ ሞት ማለት ነው!›› አለ፡፡
አባባሉ አንጀቴን በላው፡፡ ደግሞም አደነኩት፡፡ በልቤ ውስጥ የነበረችኝን ይቅርታ አንድም ሳላስቀር አውጥቼ
ሰጠሁት፡፡ ኪሴ ውስጥ ገንዘብ ቢኖረኝ ኖሮም ልስጥህ ባልኩት ነበር፡፡ በውነቱ አንድ ኢትዮጵያዊ ወጣት ከዘፋኝ
ተከታይነት ወጥቶ በራሱ ፍልስፍና እየኖረ የሶቅራጥስን የሚያክል ጥቅስ ሲናገር መስማት የደስታ ለቅሶ ያስለቅሳል፡፡
ሆኖም በወቅቱ በአዲሱ የሊዝ አዋጅ ምክንያት አጎቴ ቤቱን በተከራዩ ስለተቀማ ለቅሶ ላይ ስለነበርኩ እና እንባዬንም
ስለጨረስኩት ሳላለቅስ ቀረሁ፡፡
‹‹በጣም አመሰግናለሁ!›› አልሁት፡፡
‹‹ማመስገን ያለብኝማ እኔ ነኝ፡፡ ይገርምሃል ያኔ እስከሰላሌ ሜዳ አንተን ከማባረራችን በፊት እኔና ጓደኛቼ ወንድ
ልጅ አባረን አናውቅም ነበር፡፡ ሴት ነበር የምናባርረው፡፡ በዚህ የተነሳ ፒያሳን እንጂ ሰላሌ ሜዳን አናውቀውም
ነበር፡፡ አንተን ከማባረራችን በፊት እኔም ጓደኞቼም ከአዲስ አበባ ወጥተን አናውቅም፡፡ በተለይ እኔ ከአዲስ አበባ
ውጭ የማውቀው ሩቅ አገር ቃሊቲ ነው፡፡ ዛሬ ግን ዕድሜ ላንተ ታሪከ ተቀዬረ፡፡ ጧት እንጦጦ ብትመጣ እኔን
አታጣኝም፡፡ እንጦጦ ብታጣኝ እንኳ ሰላሌ ሜዳ ታገኘኛለህ!›› ሲል አብራራ፡፡
‹‹እንዴት?›› ስል ጠየኩ፡፡
‹‹ያኔ አንተን ሳባርር ነው እግዜር የሰጠኝ ተሰጥኦዬ ሩጫ መሆኑን ያወኩት!››
‹‹ግንኮ ሮጥክ እንጂ አልያዝከኝም?!››
‹‹ባልይዝህም ሯጭ መሆኔ ገባኝ፡፡ እናም እሮጥ ጀመር፡፡ ዛሬ በክለብ ታቅፌ ክለቤና አገሬ የሚመኩብኝ ሯጭ
ሆኛለሁ!›› አለ፡፡
በውነቱ እጅግ በጣም ደስ አለኝ፡፡ አንድ ያገሬ ልጅ እኔን ተመስሎ ተሰጥኦውን ሲያገኝ እንዴት አልደሰት፤ ለዛውም
ሩጫን የመሰለ ተሰጥኦ፡፡ ከራስ አልፎ አገር የሚያስጠራ ታላቅ ሙያ፡፡ እግዜር አንድን ሰው ሊለውጥ ሲፈልግ መልዓኩ
ገብሬልን ነው የሚልከው፡፡ አንዳንዴ ሳስበው ግን እኔንም ይልከኛል መሰል፡፡
‹‹በነገርህ ላይ ያኔ ስታሯሩጡኝ አንድ የረሳችሁት ነገር ነበር!›› አልሁት፡፡
‹‹ምን?››
‹‹እኔም እንደናንተ የቴዴ አፍሮ ዘፈኖች አድናቂ መሆኔን፡፡ ልዩነቱ እናንተ ሰውዬውን እኔ ሙዚቃውን መውደዳችን
ነው፡፡ እግዚሃር በየለቱ በሚጎበኛት አገር የሰው ጣኦት መፍጠር ጥሩ አይደለም፡፡ በጋኔን ያስመታል!›› አልኩት፡፡
‹‹እግዜር ኢትዮጵያን በየለቱ ይጎበኛታል ብለህ ታምናለህ እንዴ?››
‹‹ሌላ ምን ምርጫ ይኖረዋል፡፡ ወደ ሰሜን ቢያይ አመፀኛ፤ ወደ ደቡብ ቢቃኝ የባህር ወንበዴ፣ ወደ ምዕራብ ቢያማትር
ግብረሰዶማዊ፤ ምስራቅ ቢያቀና አላውቅህም የሚለው ትውልድ ይገጥመዋል፡፡ አንገቱን ነቅንቆ ወደኛው ይመለሳል፡፡
አያያዙን ስተነው እንጂ የዘመኑ አብርሃሞች እኛ ነበርን!›› አልኩት፡፡ የሰማኝ አልመሰለኝም፡፡
‹‹ይገርምሃል፡፡ ዘፈን ከመውደዴ የተነሳ ዘፋኝ ማምለክ ጀምሬ ነበር፡፡ ይሄ ራስን መናቅ ከእግዜር መራቅ መሆኑ
ሲሰማኝ ራሴን ጠላሁ፡፡ ተፀፀትኩ፡፡ የሩጫ ክህሎቴ ደግሞ አፅናናኝ!›› አለ፡፡
‹‹ጥሩ አድርገሃል፡፡ ያኔ ግን ብትይዙኝ ኖሮ ምን ታደርጉኝ ነበር?›› ስል ጠዬኩ፡፡
‹‹እንደ መጥምቁ ዮሃንስ አንገትህን እንቆርጠው ነበር፡፡ የሄሮድስ እርኩስ መንፈስ በዘፈን ታዝሎ አናታችን ላይ
ሰፍሮ ነበር!›› ሲል መለሰ፡፡
ዘገነነኝ፡፡ ‘’ገረፍ ገረፍ አድርገን እንለቅሃለን!” የሚል ነበር የመሰለኝ፡፡ ወይ ጉድ፤ ከሞቴ አሟሟቴ፡፡ አገሬ
በሴቶች ጉዳይ ብቻ ትጨነቃለች፡፡ እንዲህ አይነት የወንዶች ጉዳይ መኖሩን ሳታውቅ፡፡ አይ የዛሬ ልጅ፤ አባቶቹ
ለእናት አገራቸው ፈረንጂ ሲገሉ ቢያይ እሱ ለዘፈን እኔን ወንድሙን ሊገድል ተነሳ፡፡ በዚህ የተነሳ ‘’አለም ላይ
የመጀመሪያው ማህበራዊ ብርሃነ ህሊና (social enlightenment) የታዬው በኢትዮጵያ ሲሆን የመጨረሻው
ማህበራዊ ዝቅጠት (social depression) የተከሰተውም በዚችው በኢትዮጵያ ነው’’ ብለው የፃፉትን
ምዕራባውያን ፀሃፍት ላምናቸው ወሰንኩና ከአርበኝነቴ ጋር ስለማይሄድ ተውኩት፡፡ ግን በጣም ነበር የከፋኝ፡፡ እስኪ
አንባቢያን አስቡት፤ በዘፈን ሰበብ የሞት እጩ ሆኖ ከመቅረብ የባሰ ምን አስከፊ ነገር አለ?!
‹‹ብቻ ግን ገብሬልዬ ጠበቀን፡፡ ትዝ ይልህ ከሆነ ያኔ ያሯሯጥንህ በገብሬል ዕለት ነበር፡፡ ሰው ከመግደል
የዳንኩበት ሩጫ እንደምችል የተረዳሁበት ቀን ስለሆነ በየወሩ ገብሬልን እዘክራለሁ፡፡ በመጭው ገብሬል የትም
እንዳትሄድ እኔ ቤት ነህ፡፡ ዳቦ ትቆርሳለህ!›› አለ፡፡
‹‹በል በየወሩ በ19 እቤትህ አልቀርም፡፡ በውነቱ ከቴዲ አፍሮ ወደ ገብሬል ያደረከው ሽግግር ወይም ዕድገት የፎቅ
እንጂ የአስተሳሰብ ዕድገት ለማይታይባት አገራችን አስደናቂ ዕድገት ስለሆነ በታላቅ ምሳሌነቱ አገር ቢያውቀው ምን
ይመስልሃል?›› አልኩት፡፡
‹‹ጥሩ ነው፡፡ ፃፈው፡፡ ይሄን ለለውጥ የተዘጋ ህዝብ በደንብ ስደብልኝ ደ’ሞ፡፡ ምነው እንዳንተ መፃፍ በቻልኩ ልክ
ልኩን እነግረው ነበር!›› አለ፡፡
‹‹ãረ በገብሬል ይዤሃለሁ፤ ህዝብ እንደዚህ አይባልም፤ ህዝብ እኮ እግዜር ማለት ነው?!›› አልኩት ኮስተር እና
ኩምትር ብዬ፡፡
‹‹ãረ እባክህ! እሱን ብሎ እግዜር፡፡ ለነገሩ ቢሰድቡትስ ይሰማል ብለህ ነው፡፡  በፓርላማ መዶሻና እና በዘፋኝ
ማይክራፎን ደንቁሮ!››
‹‹አንተ ራስህን ከለወጥክ ይበቃል፡፡ ሌላውም እንዳንተ ሲለወጥ ባንድ ላይ አገር ይለወጣል፡፡ ሒሳቡ እንደዚህ
ነው፡፡ ከዚህ ወዲያ ራስህን እንጂ ሰው አትከተል!››
‹‹አዎ፡፡ በተለይ ዘፋኝ አልከተልም፡፡ ዘፋኝን ብትከተለው ጥሩ ቦታ ወሰደህ ቢባል  ስቱዲዮ ነው፡፡ እንደ ስቱዲዮ
የጠበበ የአለም ክፍል ደግሞ የለም፡፡ የኮንዶሚኒዬም ጠባቡ እንኳ ስቱዲዮ ይባላል፡፡……›› አለ፡፡
የመሳቅም የማውራትም ስሜት አንድ ላይ መጣብኝ፡፡ ማውራቱን አስቀደምኩ፡፡
‹‹በዚህ እንኳን አልስማማም፡፡ አንዳንዴ ከጠባቡ የስቱዲዮ አለም የሚወጡ ዘፈኖች ለአለም መፍትሄ ሲያመጡ ታይቷል፡፡
ጦርነትና ሰላም ያልፈታውን ዘፈን ፈቶት ያውቃል፡፡ ለምሳሌ የቴዲ አፍሮ ‘ኻብ ዳህላክ’ የተቆረጠ የኢትዮጵያን ብርሌ
አንገት መልሶ የሚቀጥል ይመስለኛል!›› አልኩት፡፡
‹‹………ብለን ተስፋ እናድርጋለን፡፡ ዘጠና ዘጠኝ ከመቶ ያገሬ ዘፈን ግን ከአንሶላ ውስጥ ወግ አልወጣም፡፡ የአንሶላ
ውስጥ ወግ ከኦርጋዝም ዘዴ በስተቀር ምን ይነግርሃል!? ለሱ ለሱማ እኛም አናንስም….›› አለ፡፡  በጣም ሳኩ፡፡
‹‹ወደፊት ከአንሶላ ወጥተው እንደሚዘፍኑ ተስፋ እናደርጋለን!››
‹‹ብርዱን ይችሉታል ብለህ ነው?››
‹‹ቴዲ አፍሮ ከአልጋ ወርዶ ከቤተመንግስቱ ማማ ላይ ወጥቶ በመለስ መላጣ አንዣቦ ቀጥሎም ቃሊቲ ገብቶ ብርዱ
እንደሚቻል ያሳያቸው መሰለኝ!››
‹‹አይ፤ የቃሊቲን ብርድ እንኳ እንዳልቻለው አረጋግጠናል፡፡ ቃሊቲ የፖለቲካ አቋሙን አስለወጠው እንጂ ምን ሰራለት››
‹‹በአስራ ሰባት መርፌ የጠቀመው ቁምጣ ለውጥ ካላመጣ እኔ የአቋም ለውጥ ላምጣ ብሎ እንደሆንስ?››
‹‹አይመስለኝም፡፡ ነገሩ ሌላ ነው፡፡ በቴዲ አፍሮ የፖለቲካ አቋም ውስጥ ፍቅር ፊቸሪንግ ገባኮ!››
‹‹ምንድን ነው የምታወራው?››
‹‹የቴዲ አፍሮ ጊዜያዊ የፖለቲካ አቋም ለፍተሻ ወደ ተቃዋሚ ላቦራቶሪ መውረድ አለበት፡፡ የሁለት መቶ ሺ ብር
የአልማዝ ቀለበት ለፍቅረኛው ማሰሩን ሰማህ ደ’ሞ?!››
‹‹አይ፤ ከመርካቶ የጎዳና ህፃናት ጋር ፋሲካን አብሮ ቢውል አይሻልም ነበር፤ ነፍሱንም ዝናውንም አንድ ላይ
ለማስኬድ?!››
‹‹ማን ይምከረው፡፡ ምን የዛሬ ዘፋኝ እሱ መካሪ፤ ራሱ ተመካሪ፤ ራሱ አርቲስት፤ ራሱ ሳይንቲስት፤ ራሱ ገጣሚ፤ ራሱ
ዜማ ከግጥም አጋጣሚ፤ ራሱ ኪቦርዲስት፤ ራሱ ጊታሪስት፤ ራሱ ዘፋኝ፤ ራሱ ዘማሪ፡፡ እንደ መድሃኒያለም በአንድ ጊዜ
በሁሉ ቦታ እየተገኘ ቄሳርና እየሱስን አምታታብን’ኮ፡፡…..››
‹‹ይገርማል!››
‹‹እንዳው የምሩ ግን፤ ግለሰብ ግንባታ፣ ማህበረሰብ ግንባታ እና ሙዚቃ እንደ ስላሶች የተዋሃዱ አይመስልህም፤ በዚች
ምስኪን አገራችን? የአገሬ ሰው ሙዚቃን ቅዱስ መንፈስ አድርጎ በትዝታ፣ አንቺዬና አንቺ ሆዬ ሲቆዝም ይውላል፡፡
ከእግዜር ርቆ፤ ከስራ ርቆ፤ በእውኑ ተርቦ፤ በህልሙ ቅቤ ጠጥቶ የውሸት ሲኖር ሳይ እዝናለው፤……›› አለ፡፡
‹‹እንዲህ ትፈላሰፋለህ እንዴ?››
‹‹ትንሽ እውቀት አደገኛ ስለሆነ ይሆናል የሚያፈላስፈኝ፤…..››
‹‹ትንሽ የሚባል ዕውቀት የለም፡፡ ያለችህን ባግባብ ከተጠቀምክ አንተ አዋቂ ነህ፡፡ ለምሳሌ ቴዲ አፍሮ ያለችውን
ዕውቀት በመጠቀሙ የሙዚቃውን ምህዳር በራሱ ሰሌን ጠቀለለው፡፡ ከዚህ ወዲያ ቴዲ አፍሮ በዘንድሮው አልበሙ በመዝፈን
ፋንታ ዘነጠብን ብለህ ብታወራ ምቀኛ ነህ!›› አልኩት፡፡
‹‹ዘንድሮ ቀሽም ዘፈነ እንዴ?››
‹‹የአቤል ሙሉጌታንና ሃይሌ ሩትን ዘፈን ከመስማትህ በፊት ከሰማኸው በርግጥ አሪፍ ነው፡፡ ቴዲ አፍሮ የሃይሌን
አቤልን ዘፈን ሳይሰማ አልበም ማውጣቱ ሳይጎዳው አልቀረም፡፡ ባገሪቱ የሙዚቃ ባለሙያ ከሌለ እኛው እንተንትነው
እንጂ!…..››
‹‹ወይ ጉድ፤ አንተ ነገረኛ ነህ፡፡ እስኪ እኔም እሰመዋለሁ፤….››
‹‹እስካሁን ሳትሰማው? እውነትም ጨክነሃል!››
‹‹ከቴዲ አፍሮ ዘፈን ይልቅ የቴዲ አፍሮ የ200 ሺህ ብር የጣት ቀለበት ወሬ ነው የመሰጠኝ፤…..፡፡ እስኪ አስበው
ረሃብ ጥርስና ጥፍር አውጥቶ የአዳሜና ሄዋኔን ጨጓራ ሲቧጥጥ በሚውልበት አዲሳባ፤ 200 ሺ ብር አንድ ኢንች
ዲያሜትር ቀለበት ሆኖ፤ ከአንድ አለንጋ ጣት ላይ እንደዋዛ ተሰንቅሮ ያለስራ ሲወዛዎዝ ሲውል ስታይ ፃፍ ፃፍ
አያሰኝህም?›› አለ፡፡
‹‹አንተን ሩጥ ሩጥ አሰኘህ እንዴ?›› ብዬ አሳኩት፡፡
‹‹እውነት እንደ ጋዜጠኛ ይሄ ነገር አያሳስብህም?›› አለ ቀጥሎ፡፡
‹‹በርግጥ ያሳስበኛል፡፡ አንዳንዱ የዚህ ዘመን ፍቅር እንደ ኤሌክትሪክ በማዕድን በኩል ካልሆነ ወደ ልብ አልሄድም
እያለ ችግር ሆነኮ፡፡ ቴዲዬን እሱ ነገር ገጥሞት እንደውሳ፡፡ አትፍረድ፤ ይፈረድብሃል፡፡ ደግሞ ኦሾ ምን ብሏል
መሰለህ፤ ‘ፍቅር እምቢ ካለህ በአልማዝ ቀለበት ምጣበት፤ ልኩን ያገኛል!’››
‹‹ኦሾ እንዲህ አለ እንዴ በናትህ?›› አለ እዬሳቀ፡፡
‹‹ሳይል አይቀርም ብዬ ነው፡፡ መቼስ ኦሾ የማይለው ነገር የለ!››
‹‹እየቀለድክ ነው መሰለኝ፡፡ …….አናዳጁ ነገር ደግሞ ምን መሰለህ?››
‹‹ምንድን ነው?››
‹‹ከጠቅልል ሚኒስትራችን ጋር እኮ ነው ተዛምዶት ያረፈው?!›› አለ ድምፁን ቀነስ አድርጎ፡፡
‹‹እኮ ቴዲ አፍሮ?›› አልኩ ጮክ ብዬ፤ ክፍት አፍ የሆንኩ ልጅ፡፡ እንዳው ምን ይሻለኛል?!
‹‹ታዲያስ!››
‹‹በተሰቀለው! በየት በኩል ባክህ?››
‹‹በናታቸው በኩል ነው አሉ!››
‹‹ሆ ሆ…..ይሄ ነገር እንዴት ነው፡፡ የቀጣዩ አልበም መጠሪያ  ‘ህዳሴው’  የሚል ይሆናል በለኛ!››
‹‹’ብሄር ብሄረሰብ’ ሊባልም ይችላል፡፡ እንደ ሮያል ቤተሰቡ ስምምነት ነው!››
‹‹ወይ ነገር፡፡ እንደ ሰለሞን ተካልኝ ‘ቅንድቡ’ የሚል ነጠላ ለቆ ጉድ እንዳያሰማን እንጂ እባክህ!››
‹‹ያኔማ እስከ ቀይ ባህር ድረስ ነው የማሯሩጠው፡፡….››
‹‹ይሄን ሁሉ መረጃ ግን የት ነው የምታገኘው?›› ስል ጠዬኩ፡፡
‹‹ፌስ ቡክ ነዋ፡፡ ፌስቡክ አያመጣው የለ፡፡ ሰሞኑንማ ተወው፡፡ ፌስቡክህን በከፈትክ ቁጥር ቴዲ አፍሮ ቆሞ፤ እጩ
ባለቤቱ ተቀምጣ፤ በግራ፣ በቀኝ፣ በኋላ፣ በፊት፣ በታች፣ በላይ፤ ወዘተ… ሲሳሳሙ ታያለህ፡፡ ይሄ እውነት ቴዲ
ካሳሁን ነው? ብለህ ልትጠራጠር ሲያምርህ ያቺን ውብ ፈገግታ ብልጭ አድርጎ ‘’አትጠራጠር እኔ ነኝ’’ ይልሃል
ቴዲዬ፡፡ ወይ ጉድ ብለህ ወይም ቀንተህ ወይም በጉምጃት ምራቅህን እንዳትጨርስ ሰግተህ ፌስ ቡክህን ትቆልፍና
ኢሜልህን ስትከፍት የማታውቀው ሰው ሰበር ዜና ብሎ ‘’ቴዲ አፍሮ ቀለበት አሰረ’’ ይሉት ሰባራ ዜና ይልክልሃል፡፡
ምርር ብሎህ ኤሜልህንም ፌስቡክህንም ጠርቅመህ ኖትቡክህን ገልጠህ እውቀት ለመመርመር ቁጭ ባልክበት ስራ ያጣው ቴሌ
የማይመለከትህን ሜሴጅ ይሰድልሃል፤ ብረትን ወርቅ የሚያደርጉ ወርቅ የሆኑ አልኬሚስት ዘመዶቻችን የመሰረቱት ሙዚቃችን
ሊያሳድግ ሊመነድግ የተነሳው አዲሱ የቢዝነስ ሞኖፖሊ የቴዲ አፍሮን ዘፈን ግዛ ይልሃል፡፡ መፅሃፍ ግዛ አይልህም
እኮ፤ መፅሃፍ ከገዛህማ ትበልጠዋለሃ፤ ካርል ማርክስን እየጠቀስክ ሞኖፖሊውን ድባቅ ትመታበታለሃ፤ ስለዚህ በዘፈን
ሊያዘናጋህ ይፈልጋል፤…..›› አለ በምሬት፡፡
‹‹አዲሱ ካፒታሊስት ሙዚቃችን ሊያሳድግ ቢነሳ አታሽሟጠው!›› አልኩት፡፡
‹‹አሁን ገና ልበልጥህ ነው፡፡ ልብህ ሳታድግ፤ ሳንባህ መጠኑ ቢጨምር የካንሰር ተጠቂ ትሆናለህ፡፡ በጣም እርቦህ
ሙዚቃ ሰምተህ ታውቃለህ? ረሃብህ እጥፍ ይጨምራል፡፡ የአገሬ ዘፈን አድጎ የአገሬ ህዝብ በአስተሳሰቡ በቆመበት
የሚረግጥ ከሆነ ማህበራዊ ካንሰር ተከሰተ ይባላል፡፡ ቴዲ አፍሮ ሚስት በማጨቱ አንዳንድ የአገሬ ሴቶች በብስጭት
በረኪና ካልጨለጥን ካሉ ካንሰር ማለት ይሄ ነው፡፡..…›› ሲል መለሰ፡፡
‹‹በጣም የመረረህ ትመስላለህ?›› አልኩት፡፡
‹‹እንኳን እኔ የፌስቡክ መስራች ማርክ ዙከርበርግ ራሱ ሳይመረው አልቀረም!››
‹‹እንዴት? ደሞ እሱ ምኑ ተነካና?››
‹‹የመሃመድ ቦአዚዝ አብዮት በአረቡ አለም፤ የቴዲ አፍሮና የእጮኛው ፎቶ ሾፕ በአበሻ አለም ፌስቡኩን
ሲያጨናንቁበትሳ!?›› ሲል መለሰ፡፡ እዚህ ላይ ጦሽ ብዬ ነበር የሳኩት፡፡
‹‹ለማንኛውም የአብርሃምና የሳራ ጋብቻ እንዲሆንለት ልመኝ መሰል!›› ሲል ቀጠለ፡፡
‹‹የፀጋዬ እና ፊያሜታን ፍቅር ያድርግለት ማለት አይሻልም?!››
‹‹ፀጋዬና ፊያሜታ እነማ ናቸው ልልህ ነበርኮ፡፡ ኦሮማይን ማንበቤ ትዝ አለኝ፡፡ በነገርህ ላይ የቴዲ አፍሮ ጥምረት
እኔን ጨምሮ የበርካታ ወንዶችን የሞራል ጥያቄ የመለሰ በመሆኑ በአንድ በኩል ይደነቃል!›› አለ፡፡
‹‹እንዴት?››
‹‹እንደምታዬኝ አጭር ነኝ፡፡ ረጂም ሴት አግብቼ ነበር፤ ኋላም ፈታቺኝ፡፡ የሰፈር ሰው ባለፍን ባገደምን ቁጥር
‘ፈረስና ባልደራስ’ እያለ በሽሙጥ ፍቅራችን ደመሰሰው፡፡ ረጂም ሴት ላላገባ ማልኩ፡፡ ረጂም ሴት ለማግባት አጭር
ወንዶች የሚፈሩት ለምን እንደሆነም ገባኝ፡፡ በዚህ በኩል ቴዲ አፍሮ የቁመት ባልደረቦቹን ነፃ ሳያወጣን
አልቀረም!›› አለ፡፡
‹‹ሴቶችኮ ወርቅ ልብ ማዬት ካልቻሉ ወርቅ ማዕድን፤ ወርቅ ማዕድን ማዬት ካልቻሉ ወርቅ ልብ ያያሉ እንጂ ቁመት
አያዩም፡፡ ሚስትህ የፈታችህ በሰፈር ሽሙጥ በቀላሉ የሚታጠፍ ሽቦ ልብህን አይታ እንጂ በቁመትህ ማጠር
አይመስለኝም!›› አልኩት፡፡
ደስ አለው፡፡ ተንደርድሮ መጥቶ ግንባሬን ሳመኝ፡፡
‹‹ከአመታት በፊት በቦክስ ልትተረትረው የነበረውን ግንባር አሁን ስትስመው ምን ተሰማህ›› አልኩት፡፡
‹‹ሃሴት ነዋ! ሃሴት!››
የጠጣሁትን ሻይ፤ የበላሁትን ኬክ ከፈለ፡፡ ‹‹ከሳምንት በኋላ ለውድድር ወደ ኦስሎ ኖሮዌይ እሄዳለሁ፡፡ ስመለስ
እደውልልሃለሁ!›› ብሎ ስልኬን ተቀበለ፡፡
‹‹ስንት ሺ ሜትር ነው የምትሮጠው?›› ስል ጠዬኩት፡፡
‹‹5 ሺ››
‹‹በል የቀነኒሳን ሪከርድ እንዳትሰብር ተጠንቀቅ!›› አልኩት:: (መቼስ የቀነኒሳ ነገር አይሆንልኝ፡፡ ቀነኒሳን
ሰሞኑን አይታችሁታል ወይ? ãረ ኦሎምፒክ ደርሷል ንቃ በሉት፡፡ ያያችሁት ካላችሁ አደራ ንገሩኝ፡፡ ናፍቆኛል፡፡
አቤት ስወደው፡፡ እዩኝ አይል፤ ስሙኝ አይል፤ ሳሙኝ አይል፤ ካልፈረምኩላችሁ አይል፤ ተደብቆ ከርሞ ይመጣና ሪከርድ
ሰብሮ ልማታዊ አርቲስት የሰበረውን ቅስማችን ይጠግንልናል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ አንዱ ሲሰብረው አንዱ እየደረሰ
ባይጠግነው ኖሮ ምን ይውጠው ነበር? ወገኔ ግን ሞኝ ነው፤ ከጠጋኙ ትቶ ከሰባሪው ጋር ይውላል፡፡ በሬ ካራጁ
እንደሚውለው፡፡)
‹‹ለምንድን ነው የቀነኒሳን ሪከርድ እንዳልሰብር የፈለከው?›› ብሎ ጠየቀ፡፡
‹‹ቀስ ብሎ ማደግ አይሻልም? ቶሎ ማደግ እኮ ነው አገር የፈታው፡፡ ቀርቀሃ ከወይራ ቀድሞ ያድግና በነፋስ ዝንጥፍ
ብሎ ይወድቃል!›› ብዬ መለስኩለት፡፡
ሳቀ፡፡
‹‹እንደ ቀነኒሳ አሸንፈህ አስፈንጥዘን በናትህ!›› አልኩት ቀጥሎ፡፡
‹‹አትጠራጠር፡፡ ይልቅ ስመለስ አበባ ይዘህ ኤርፖርት እንድትጠብቀኝ!›› አለ፡፡
‹‹ከቴዲ አፍሮ ጋር ማይክ ይዘን እንጠብቅሃለን፡፡ እኔ ለቃለመጠይቅ እሱ ሊዘፍንልህ!›› አልኩት፡፡
እየሳቀ ሄደ፡፡ ቀጥሬው የነበረው ጓደኛዬ ከርቀት ሲመጣ አየሁት፡፡ ከቀጠሮው ሰዓት በጣም ዘግይቶ ነበር፡፡ እንኳንም
ዘገዬ፡፡ እሱ ባይዘገይ ኖሮ ይሄ ወሬ ባልተፃፈ ነበር፡፡